ዩኒቨርሲቲው የውስጥ ለዉስጥ የመንገድ ግንባታ ስራ ለማስጀመር ከአሸናፊዉ ድርጅት ጋር ዛሬ ዉል ተፈርርሟል፡፡
የተፈረመው ውል ከ6 ኪሎ ሜትር በላይ የሆነ የውስጥ ለውስጥ መንገድ አስፋልት ግንባታ ስራን ያካትታል።
ተቋራጩ በአጭር ጊዜ ውስጥ የመንገድ ግንባታዉን አጠናቅቆ ለማስረከብ ዉል የገባ ሲሆን ሲጠናቀቅ ለተማሪዎች ፣ መምህራን እና ለሰራተኞች እንዲሁም ለአካባቢዉ ማህበረሰብ ምቹ የትምህርት አካባቢ ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተገልጿል፡፡
በተያዘዉ የበጀት ዓመት ዩኒቨርሲቲው 4.4 ኪሎ ሜትር አጥር ግንባታ የሚሸፍን ስራ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን የዩኒቨርሲቲውን ደህንነትና አስተዳደር አቅም የሚጠናክር እንደሆነ ተጠቅሷል።
ዉል ስምምነቱም በዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ከማል አብዱራሂም እና በክሮስላንድ ኮንስትራክሽን ማኔጂንግ ዳይሬክተር በአቶ ወልዴ ዘሪሁን ተካሂዷል፡፡
ስራው የሁሉምን ባለ ድርሻ አካላት ትብብር የሚጠይቅ በመሆኑ ሁሉም ድርሻውን እንዲወጣ ተጠይቋል።
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን
Twitter:Assosa University (@AssosaU) / X
WhatsApp group: https://whatsapp.com/channel/0029Vau844l9xVJkZ3GXR21P
Telegram: https://t.me/+J9ZDxvCigO0yN2Nk
Email: pir@asu.edu.et


