የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ዛሬ ባካሄደዉ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አሳልፏል፡፡
ሴኔቱ በአንደኛ አጀንዳዉ የዩኒቨርሲቲው የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርታቸዉን ሲከታተሉ ለነበሩ የመደበኛ፣ የሳምት መጨረሻ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎችን ዉጤት እንዲሁም የመጀመሪያ ዓመት የተማሪዎች የዲፓርትመት ምደባ በሬጅስተራር ጽ/ቤት ሃላፊ በዶ/ር ሀብታሙ ሸንቁጥ አቅራቢነት በመገምገም ስታተሱን አፅድቋል፡፡
ሴኔቱ በመቀጠል የተመለከተዉ የዩኒቨርሲቲዉን የሰኔት መተዳደሪያ ደንብ (Senate Legislation) ክለሳ በአዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር የሪፎርም ስራዎች መሠረት በመቃኘት የተደረጉ ማስተካከያዎችን ተወያቶ አፅድቋል፡፡
በሦስተኛ ደረጃ ሴኔቱ የተመለከተዉ አጀንዳ የከፍተኛ ትምህርት የኦን ላይን ትምህርት
( Electronic Learing) የአፈፃፀም መመሪያን ደንብ ቁጥር 1044/2025 ተወያይቶ አፅድቋል።
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን
Twitter:Assosa University (@AssosaU) / X
WhatsApp group: https://whatsapp.com/channel/0029Vau844l9xVJkZ3GXR21P
Telegram: https://t.me/+J9ZDxvCigO0yN2Nk
Email: pir@asu.edu.et




