የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት የሬሜድያል ተማሪዎች ቅበላ፣ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ውጤት ማፅደቅ እና የዩኒቨርሲቲው መሪ ቃል አመራረጥ ዙሪያ ተወያይቶ ዉሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በስብሰባው የ2017 ዓ/ም የሬሜዲያል ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ጥር 22- 23 2017 ዓ/ም እንዲሆን ወስኗል፡፡በተጨማሪም በሁለተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ውጤት አጽድቋል፡፡
በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲውን መሪ ቃል በተመለከተ ለዩኒቨርሲቲው እና ለአካባቢው ማህበረሰብ ለውድድር ቀርቦ ምርጫ እንዲካሄድ ሴኔቱ ወስኖ ስብሰባው ተጠናቋል።
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን
Twitter:Assosa University (@AssosaU) / X
WhatsApp group: https://whatsapp.com/channel/0029Vau844l9xVJkZ3GXR21P
Telegram: https://t.me/+J9ZDxvCigO0yN2Nk
Email: pir@asu.edu.et
Instagram: https://www.instagram.com/asueduet/#


