Assosa University

የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ልኡካን ቡድን አሶሳ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት

በ10ኛው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ሲሳተፍ የነበረው የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ልኡካን ቡድን አሶሳ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
 
በጅማ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ከጥር 17 እስከ የካቲት 1/2018 ዓ/ም ድረስ የመላ ኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የስፖርት ዉድድር “ስፖርት ብዝሃነትና ዕውቀት ለልህቀት!” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ መቆየቱ ይታወሳል።
 
ልኡካን ቡድኑ በዚሁ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በተሳተፈባቸው የተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች የስፖርታዊ ጨዋነትን በማሳየት ላደረገዉ ብርቱ ዉድድር የብዙዎችን ቀልብ የሳበ ሲሆን በሴቶች የቼዝ ጨዋታም የወርቅ ሜዳሊያ አግኝቷል፡፡
 
በዚህ የአቀባበል ስነስርአት ላይ የሚመለከታቸዉ የዩኒቨርሲቲዉ አመራሮችን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችና ሠራተኞች ደስታቸውን በመግለጽ ተቀብለዋቸዋል።
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን
Twitter:Assosa University (@AssosaU) / X
Email: pir@asu.edu.et

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *