በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የሮመዳን ፆም ምክኒያት በማድረግ የዩኒቨርስቲው አመራሮች ከተማሪዎች ጋር የኢፍጣር መርሃ ግብር በተማሪዎች ምግብ ቤት አካሂደዋል::
በመርሃ ግብሩ ላይ የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ መ/ር ንጋቱ ሀምቢሳ ተገኝተው የፍቅርና የመተሳሰብ ጊዜ ለሆነው የሮመዳን ወር የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።
እንዲሁም የተማሪዎች መሰ/አገ/ ዲን መ/ር ጌታቸው ገለታ እና የሴ/ት ማህ/ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ መ/ርት መርቀኒያ አሊ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ተማሪዎችን አበረታትዋቸዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ተማሪዎችም ለተደረገላቸው የአፍጠር ፕሮግራም ተደስተው ዩኒቨርሲቲውን አመስግነዋል።
የተቋሙን ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፤
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን
Twitter:Assosa University (@AssosaU) / X
WhatsApp group: https://whatsapp.com/channel/0029Vau844l9xVJkZ3GXR21P
Telegram: https://t.me/+J9ZDxvCigO0yN2Nk
Email: pir@asu.edu.et
Instagram: https://www.instagram.com/asueduet/#