(የካቲት 17/2015 ዓ/ም) የግንባታ ዉል አስተዳደርን አስመልክቶ የዩኒቨርሲቲዉ የግንባታ አማካሪዎች፣ የፕሮጀክት ጽ/ቤት እና በቀጥታ ከሚመለከታቸዉ የስራ ክፍል ሃላፊዎች ጋር ዉይይት ተደረጓል፡፡
ለዉይይት መነሻ የሚሆን በህግ ት/ቤት መምህር በሆኑት ዘሪሁን ይታየዉ የኢትዮጵያ የግንባታ ዉል አስተዳደር እና የጨረታ ህግን አስመልክቶ የወጡ አዋጆች፣ መመሪያዎች እና ደንቦችን ቀርበዉ በሰፊዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
አማካሪዎች፣ የፕሮጀክት ጽ/ቤት ሰራተኞች እና በቀጥታ የሚመለከታቸዉ ስራ ክፍሎች በተቋራጮች የሚከናዉኑ የግንባታ ስራዎች የግንባታ ዉል እና መመሪያዎችን በመጠበቅ መስራት እንደሚገባ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ከማል አብዱራሂም በዉይይቱ ላይ አሳስበዋል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን
Twitter:Assosa University (@AssosaU) / X
WhatsApp group: https://whatsapp.com/channel/0029Vau844l9xVJkZ3GXR21P
Telegram: https://t.me/+J9ZDxvCigO0yN2Nk
Email: pir@asu.edu.et
Instagram: https://www.instagram.com/asueduet/#