


አሶሳ ዩኒቨርሲቲ ለትሮፕካል እና ተላላፊ በሽታዎች ምርምር ማዕከል ለቀረቡ የምርምር ትልሞች (ፕሮፖዛል) ግምገማ እያካሄደ ይገኛል።
የምርምር ፕሮፖዛል ግምገማዉ የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ዑመር ሸሪፍ በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን ለዚሁ ማዕከል ምርምር ሥራ የቀረቡት 6 የምርምር ትልሞች በወጣላቸዉ መገምገሚያ መስፈርት መሠረት ታይቶ ያለፉ ወደ ምርምር ሥራ እንደሚገቡ ገልፀዋል።
ግምገማዉ በዩኒቨርሲቲዉ የምርምር ማዕከላት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊ ዶ/ር ቱጌ ተመስገን የሚመራ ሲሆን ተሳታፊዎቹም የፕሮፖዛል አቅራቢዎችና የሚመለከታቸው መምህራን ናቸዉ።
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ገፆቻችን ይከተሉ
Twitter:Assosa University (@AssosaU) / X
Website: www.asu.edu.et
WhatsApp group: https://whatsapp.com/channel/0029Vau844l9xVJkZ3GXR21P
Facebook: https://www.facebook.com/AssosaUniversityOfficial
Telegram: https://t.me/+J9ZDxvCigO0yN2Nk
Email: pir@asu.edu.et